Breaking News

TimeLine Layout

April, 2019

  • 7 April

    ዖሮሞ ያልሆኑ ሰዎች በኦሮሞ ሲፈናቀሉ ተመልከቱ። ኣቢይና ለማ ይህን እያዩ ትንፍሽ አይሉም!

    ከ ቡራዩ ፣ አራት ኪሎ ፣ ለገጣፎ እና ሱሉልታ ቀጥሎ የማፍረስ እና ማፈናቀሉ ተረኛ ሰበታ ሆናለች በሰበታ ማንነታቸው እየተለየ በለሊት ቤት በላያቸው ላይ በማፍረስ የጀመሩት ድርጊት እስካሁን ከ 3500 በላይ ህዝብ ተፈናቅሏል እውነት ግን ይሄ ሁሉ ግፍ ሲፈፀም የሚያይ አይምሮ ምን አይነት ነው? ለማነውስ ነው አቤት የሚባለው?Posted by Peace Everywhere …

    Read More »
  • 4 April

    ለውጭ ምንዛሪ ክምችት ጥያቄ ማስተናገድ እንደማይቻል ታወቀ::

    ለውጭ ምንዛሪ ክምችት የተለየ መፍትሔ ካልተገኘ ከነዳጅና ከመድኃኒት ግዥ በስተቀር ሌላ ጥያቄ ማስተናገድ እንደማይቻል ታወቀ 31 March 2019 ዮሐንስ አንበርብር የልማት ባንክ የማይመለስና አጠራጣሪ ብድር 18.1 ቢሊዮን ብር ደርሷል በሦስት ወራት 344 ሚሊዮን ብር መክሰሩ ተገልጿል በቀጣዮቹ ወራት በተለየ ሁኔታ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ ካልተገኘ በስተቀር፣ ከነዳጅና ከመድኃኒት ግዥ በዘለለ የኢኮኖሚውን ፍላጎት ማስተናገድ እንደማይቻልየብሔራዊ ባንክ ገዥ አስታወቁ። የብሔራዊ ባንክ ገዥ ይናገር ደሴ (ዶ/ር) የ2011 በጀት ዓመት የስምንት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሐሙስ መጋቢት19 ቀን 2011 ዓ.ም. ባቀረቡበት ወቅት ነው ይህንን የተናገሩት። የባንኩ ገዥ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት ባለፉት ስምንት ወራት አገሪቱ ለውጭ ገበያ ከምታቀርባቸው ሸቀጦችና አገልግሎቶች የተገኘው የውጭ ምንዛሪ1.64 ቢሊዮን ዶላር መሆኑን አመልክተዋል። በተጠቀሱት ወራት ከወጪ ንግድ የተገኘው የውጭ ምንዛሪ በ2010 ዓ.ም. ተመሳሳይ ወቅት ከተገኘው መጠን ጋር ሲነፃፀር በ9.4 በመቶ ያነሰ እንደሆነገልጸዋል። ከግለሰቦችና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች የተላከ የሐዋላ ገቢ በአጠቃላይ 3.8 ቢሊዮን ዶላር እንደሆነ አስረድተዋል። በተቃራኒው ባለፉት ስምንት ወራት አገሪቱ ከውጭ ለምታስገባቸው ምርቶች 10.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ መደረጉን፣ ይህም ወጪ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይወቅት ጋር ሲነፃፀር በ1.3 በመቶ ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል። በተጠቀሱት ወራት ከወጣው የውጭ ምንዛሪ ውስጥ ለነዳጅ ግዥ የተከፈለው 1.7 ቢሊዮን ዶላር ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዝ አስታውቀዋል። በተጠቀሱት ወራት ወደ አገር ለገቡ ሸቀጦች የተከፈለው የውጭ ምንዛሪና ወደ ውጭ ከተላኩ ሸቀጦች የተገኘው የውጭ ምንዛሪ መሀል የ8.9 ቢሊዮን ዶላርየንግድ ሚዛን ጉድለት እንደሚታይ የገለጹት የብሔራዊ ባንክ ገዥ፣ የተገለጸው ጉድለት የተሸፈነው ከአገልግሎት (በዋናነት ከአየር ትራንስፖርት አገልግሎት)፣ከውጭ በሐዋላ ከተላከ ገቢና ከውጭ ከተገኘ ዕርዳታና ብድር መሆኑን አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅት ያለው መጠባበቂያ የውጭ ምንዛሪ ክምችት የ2.6 ወራት ፍላጎትን ለመሸፈን ብቻ የሚበቃ እንደሆነ ገልጸዋል።  የንግድ ማኅበረሰቡ የውጭ ምንዛሪ በተመለከተ የሚያቀርበውን እሮሮ በመጥቀስ የምክር ቤቱ አባላት ስለመፍትሔው ማብራሪያ የጠየቁ ሲሆን፣ የባንኩ ገዥበሰጡት ምላሽ በአሁኑ ወቅት ያለው የውጭ ምንዛሪ መጠን የአገሪቱን ኢኮኖሚ ለማንቀሳቀስና የግሉን ዘርፍ የውጭ ምንዛሪ ፍላጎት ለማስተናገድ የሚችልበትሁኔታ ላይ እንዳልሆነ ጠቁመዋል።  እስካሁን ድረስ ጥቅም ላይ እየዋለ የነበረው የውጭ ምንዛሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ ከተለያዩ አገሮች ጋር ተነጋግረው ማምጣት የቻሉት2.7 ቢሊዮን ዶላር መሆኑን ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥረት እንደተገኘው የውጭ ምንዛሪ ተመሳሳይ ጥረት ተደርጎ በቀጣዮቹ ወራት ተመሳሳይ ሀብትካልተገኘ ኢኮኖሚውን ለማንቀሳቀስ እንደማይቻል ገልጸዋል። “ይህ ካልሆነ ልናደርግ የምንችለው ያለውን የውጭ ምንዛሪ ለነዳጅና ለመድኃኒት ግዥ ብቻ በጥንቃቄ ማዋል ነው፤” ብለዋል። ከዚህ በመለስ ኢኮኖሚውንለማንቀሳቀስ የአምስትና የአሥር ዓመታት ስትራቴጂ ነድፎ መንቀሳቀስን እንደሚጠይቅ አስረድተዋል።  በተመሳሳይ ቀን ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ወደ መንበረ ሥልጣን ሲመጡ የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት አረንቋ ውስጥ ወድቆእንደገጠማቸው ገልጸዋል። …

    Read More »
  • 3 April

    ግንቦት 20 በመጋቢት 24 ተተክቶላችኋል::

    From: Agegnehu Kassa ግንቦት 20 በመጋቢት 24 ተተክቶላችኋል ። እኛ አማሮች ከአጋሮቻችን ጋር ይህን የዘር ፓለቲካ በፅኑ እንዋጋለን ። መዳረሻችንም አብን ነው ። Why አብን ??? **አብን የሚያምንበትና ለመታገል የሚንቀሳቀሰው አማራን አዳክሞ ኢትዮጵያን ለመበተን ከሚታገል የመለስና መለስ ወለድ የኦሮሞ ተስፋፊ ሜንጫዎችና ደጋፊዎቻቸው ጋር መሆኑ = (by the way እን ማዴቦ …

    Read More »
  • 2 April

    የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የአማራ ሕዝብ የኅልውና ጥያቄዎች 6 አበይት ጉዳዮች

    ትኩረታችን ሁሉ ዋኖች ላይ ይሁን! (ገብርዬ) ***** የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን) የአማራ ሕዝብ የኅልውና ጥያቄዎች ናቸው ብሎ የለያቸው 6 አበይት ጉዳዮች የሚከተሉት ናቸው። 1) የአማራ ሕዝብ ያልተሳተፈበት፥ ይሁንታውንም ያልሰጠበትና በአማራ ጠል ኃይሎች ተደርሶ ሕገመንግሥት የተባለው ሰነድ የሁሉንም ሕዝቦችና ዜጎች ዘላቂ ጥቅም፣ መብትና ፍላጎት ባስከበረ መልኩ እንዲሻሻል/እንዲከለስ ማድረግ፤ 2) የአማራን ሕዝባዊና ግዛታዊ …

    Read More »

March, 2019

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.