Breaking News

Classic Layout

ከአማራ ተማሪዎች ማህበር(አተማ) የተሰጠ መግለጫ!

  በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሚማሩ የአማራ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ የሚገኘውን ሥቃይ እና እንግልት አስመልክቶ ከአማራ ተማሪዎች ማህበር(አተማ) የተሰጠ መግለጫ! በሀገሪቱ መዲና አዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሚማሩ የአማራ ተማሪዎች ላይ ከአድዋ በዓል ማግስት ጀምሮ ከፍተኛ ስቃይና እንግልት እንዲሁም የመብት ጥሰት እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡የጥቃቱ መነሻ <<ለምን የአጼ ምኒልክ ምስል ያለበት ወይም ንጉሡን የሚያስታውስ ቲ-ሸርት ትለብሳላችሁ?>> የሚል የድንቁርና እና ግብዝነትን ጥግ …

Read More »

ምድራችን ካስተናገደቻቸው ዘረኛ ድርጅቶች ሁሉ ዘረኛነትን ፍጹማዊ ያደረገ ዘግናኝ የዘር ድርጅት ! / Achamyeleh Tamru

By> Achamyeleh Tamiru በዐቢይ አሕመድ የሚመራው ብል[ጽ]ግና ምድራችን ካስተናገደቻቸው ዘረኛ ድርጅቶች ሁሉ ዘረኛነትን ፍጹማዊ ያደረገ ዘግናኝ የዘር ድርጅት ነው! ዐቢይ አሕመድ በፕሬዝደንትነት ስለሚመራው ብል[ጽ]ግና ልዩ ባሕርያት ሲናገር በኢትዮጵያ ከተከሰቱ ፓርቲዎች ሁሉ አገር በቀል እሰቤ በውስጡ በመያዝ የተመሰረተ የመጀመሪያው ፓርቲ መሆኑን ገልጿል። ይህን የተናገረው ዐቢይ አሕመድ በትናንትናው እለት በዋለው ውሎ የፓርቲውን የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት “ሲያስመርጥ” ውሏል። ስ ማእከላዊ ኮሚቴ ወይም Central …

Read More »

የኦሮሞ መስፋፋት እየቀጠለ ነው:: በአዲስአበባ ቤቶች እየፈረሱ ነው !

የኦሮሚያ ፕሬዝደንት ጽሕፈት ቤት ማስፋፊያ ተነሽ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ካሳ ወይም ምትክ ቦታ ሳይሰጣቸው ቤታቸውን በሦስት ቀን ውስጥ እንዲያፈርሱ የመጨረሻ ማስጠንቀቂ ተሰጣቸው (እለታዊ የኢትዩትዩብ መረጃዎች) አዲስ አበባ ፍላሚንጎ አካባቢ እስከ ግሪክ ትምህርት ቤት ድረስ ባለው አካባቢ ለሚገነባው የኦሮሚያ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ማስፋፊያ ቦታውን እንዲለቁ ትዕዛዝ የተሰጣቸው መካከል 15 የግለሰብ ቤቶች የሚገኙ ሲሆን፣ የቀበሌ ቤቶችም ተነሽ ናቸው ተብሏል፡፡ ይህንን የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ …

Read More »

እስክንድር ነጋን ምከሩት!

  ጋዜጠኛና የሠብአዊ መብት ተሟጋች የነበረው እስክንድር ነጋ ብዙ ዋጋን የከፈለ ፣ የምናከብረውና በግለሰባዊ ስብእናውም አዛኝ ፣ ትሁት ፣ ቅንና ለቃሉ ሟች የሆነ ኢትዮጵያዊ ወንድማችን ነው። በዚሁ ሙያውና ምግባሩ ቢቀጥልና ከከፍታው አይወርድም የሁላችንም ደስታ ነበር። ነገርግን ከእስር ከተፈታ በኃላ በጋዜጠኛና የሠብአዊ መብት ተሟጋችነቱ ብሎም በከፈለው መራር ዋጋ ያገኘው የህዝብ ድጋፍና እውቅና በፖለቲካውም የሚቀጥል መስሎት በአንዳንድ ግለሰቦች ጉትጎታ ጭምር ህይወቱን ከአደባባይ …

Read More »

የአፄ ምንልክን ስም ከአድዋ ላይ የመሰረዝ ሴራ በአብይ አህመድና ጀሌዎቹ !

Amhara Media Corporation/ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን      ·  “የዓድዋ ድል በዓል ምኒልክ አደባባይ ይከበራል” የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር አዲስ አበባ: የካቲት 22/2014 ዓ.ም (አሚኮ) 126ኛውን የዓድዋ ድል በዓል በምኒልክ አደባባይ እንደሚያከብር እና ሕዝቡም በተለመደዉ መንገድ በዓሉን በአደባበዩ ለመታደም እንዲገኝ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ገለጸ፡፡ በዓሉ በምኒልክ አደባባይ እንደማይከበር የሚወራዉ ወሬም ከመረጃ ክፍተት እና አለመናበብ የመጣ ነዉ ብሏል ማኅበሩ፡፡ …

Read More »

የፓርላማው አፋኝ ህገደንቦች – የደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ብስጭት !

ፓርላማ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአሰራር ስነ ስርዓት ደንብ መሰረት አንድ አባል ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄ ለማቅረብ ከ10 ቀን በፊት ለአፈ ጉባዔ ጽ/ቤት ማስገባት ይጠበቃል። ከዚያም ከአባላት የተሰበሰቡትን ጥያቄዎች አፈጉባኤዎችና በፓርላማው የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተሰባስበው የሚፈልጓቸውን ይመርጣሉ። የተመረጡ ጥያቄዎች ለጠ/ሚ/ሩ ይቀርባሉ ማለት ነው። ከታች የተያያዙትን ጥያቄዎች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ለማቅረብ ከ15 ቀን በፊት ብናስገባም የገዢው ፓርቲ በመቀስ ቆርጦ አስቀርቷቸዋል። ፓርላማው በብዙ አፋኝ …

Read More »

ለኮሚሽኑ ከተሾሙት ዉስጥ አንድም አማራ አልተወከለም ። ዝርዝሩን ተመልከቱ !

Achamyeleh Tamiru በነውረኛነቱ ፋሽስት ወያኔን የሚያስንቀው የኦሮሙማው የአፓርታይድ አገዛዝ የኦሮሙማው የአፓርታይድ አገዛዝ ዛሬ ይፋ ባደረገው “የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች” ዝርዝር ሰብሳቢውንና ምክትል ሰብሳቢዋን ኦሮሞ ሲያደርግ ለይስሙላ እንኳን አንድም የአማራ ነገድ ተወላጅ አልተካተተም። በኮሚሽነርነት የተሾሙት የአስራ አንዱ ሰዎች “ብሔር፣ ብሔረሰብና ሕዝብነት” የሚከተለውን ይመስላል፤ 1. ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ – ሰብሳቢ – [ኦሮሞ] 2. ወይዘሮ ሂሩት ገብረስላሴ – ምክትል ሰብሳቢ -[ኦሮሞ] 3. ዶክተር …

Read More »

አቶ ፀጋ አራጌ ትኩዬ እውነቱን አፈረጡት!

አቶ ፀጋ አራጌ ትኩዬ **************** ዋጋ ከፍሎ ከአማራ ህዝብ ጎን በመቆም ታሪኩን በወርቅ ቀለም ጽፎ ለማለፍ የሚወስን ፍለጋ ስንባጅ አንድ የአሳምነው ትንፋሽ ሳናገኝ አልቀረንም። ሌላ ቁርጠኛ ብቅ ይል እንደሁ ደግሞ በተስፋ እንጠብቃለን። ሰውዬው እውነትን ተጋፍጠው በአማራ ህዝብ ስነ ልቦና ልክ ከፍታቸውን አስተካክለው ለመገኘት ቆራጥ ውሳኔ ላይ ደርሰዋል ማለት ይቻላል። ***** አቶ ፀጋ አራጌ የአማራ ብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ሲሆኑ …

Read More »

የአዳነች አቤቤ መልእክት!

እነ ወ/ሮ አዳነች አበቤ ሊያጭበረብሩን ፈልገው ወይስ ሒሳብ የማይችሉ ሆነው??? ወ/ሮ አዳነች ትናንትና በከተማው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ከቤተክርስቲያን ይዞታ ውዝግብ ጋር በተያያዘ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ “ከመሬት ጋር ተያይዞ ለሚነሣው ጥያቄ ሁሉም የእምነት ተቋማት በጋራ የፈረሙበት ባለፉት ሦስት ዓመታት 2014ን ሳይጨምር በመሥተዳድሩ የተሰጡ ቦታዎችን በተመለከተ፡- • ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ 89 ቦታዎች እና በአራት ኪሎ የሚገኘውን ባለመንትያ ሕንፃ ማስመለስን ጨምሮ ሰጥተናል፡፡ …

Read More »
Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.