Breaking News
Home / News / የፋኖና የመንግስት ድርድር!

የፋኖና የመንግስት ድርድር!

የፋኖ አርበኞችና የመንግስት ድርድር!!

አደራዳሪ ሽማግሌዎቹ አርበኛ መሳፍንት ጋር ረዥም ሰዓታትን ወስደው ተወያይተዋል። አርበኛ መሳፍንት ድርጅቱን በመወከል እውነተኛ ድርድር የፋኖ አርበኞች ፅኑ ፍላጎት እንደሆነ ነግሯቸዋል። በእርሱ በኩል መንግስት ሊፈፅማቸውና ሊያሟላቸው የሚገባ ጉዳዮችን ለሽማግሌዎቹ በዝርዝር አቅርቧል። ሽማግሌዎቹም ከአርበኛ መሳፍንት ጋር ባደረጉት ውይይት እጅግ መደሰታቸውን ተናግረዋል። ድርጅቱን በመወከል አርበኛ መሳፍንት ያቀረባቸውን ጥያቄዎች ይዘው ከመንግስት አካላት ጋር ለመነጋገር ቀጠሮ ይዘዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የተጀመረው የእርቀሰላም ጥረት እንዳይሳካ ሆንብለው በሴራ ፖለቲካ የተጠመዱ የመንግስት አካላት እንዳሉ አርበኞቹ ነግረውኛል። አላስፈላጊ ትንኮሳ እያደረጉባቸው ቢሆንም እርቀሰላሙ እንዳይበላሽ ለህዝባችን ሰላም ስንል ለግዜው መታቀብን መርጠናል ብለውኛል።

ለምሳሌ ያክል በዛሬው ዕለት ሊቦ ከምከም ወረዳ ውስጥ አርበኛ ቢተው ላይ ከየትእንደመጡ በውል ያልታወቁ ታጣቂዎች የተኩስ እሩምታ ከፍተው ሁለት ሰው አቁስለዋል። ቤትም አቃጥለዋል። ከአርበኞቹ በኩል የገጠማቸውን የአፀፋ ተኩስ መቋቋም ስላቃታቸውም ፈርጥጠው ተሰውረዋል።

አርበኞቹ እንደነገሩኝ ከሆን አንዳንድ የመንግስት አካላት በስውር የራሳቸውን ፋኖ መሳይ ፋኖ አዘጋጅተው የህዝብን ሰላም ከማወካቸው በተጨማሪ እነርሱም ላይ አሳቻ ግዜና ቦታ እየጠበቁ የደፈጣ ጥቃት ሙከራ እያደረጉባቸው ነው።

አርበኞቹ እንደነገሩኝ ይህ ሆንተብሎ እርቀሰላሙን ለማበላሸትና ጎንደርን የህገወጥ መሳሬያ ንግድ ማዕከልና የትርምስ ቀጠና ለማድረግ ታስቦ የተወጠነ ሴራ መሆኑን ስለተረዳን ጉዳዩን በጥንቃቄና በትግዕስት ይዘነዋል ብለውኛል። እነማን ይሄንን እንደሚያደርጉም መረጃው አለን ቢሉኝም ስማቸውን ከመጥራት ግን ተቆጥበዋል።

ፋኖ አርበኞችም ሽማግሌዎቹም እርቀሰላሙ እንደሚሳካ ተስፋቸው ፅኑ ነው።

ጥንቅሩ የስሚ ስሚን መሰረት አድርጎ የተሰናዳ ሳይሆን በድምፅ በተያዘ መረጃ ላይ የተመሰረተ ነው።

ሰላም ለጎንደር!! ሰላም ለአማራ!! ሰላም ለኢትዮጵያ!!

ፋኖን ይርዱ

በሁሉም አቅጣጫ ያለህ አማራ ስማ ስማ

የፀረ አማራው ኦነጋዊ የአብይ አህመድ መንግስት ቅልብ የኦሮሞ ልዩ ኃይልና የኦነግ ወታደሮችን ልኮ በአማራ ፋኖ ላይ በይፋ ጦርነት ከፍቷል።ጦርነቱ በጎጃም አማራ ፋኖዎች በፍኖተሰላም ከተማ አቅራቢያ ትላንት የተጀመረ ዛሬም ተጨማሪ የመከላከያ ወታደር መጥቶ ተራግፏል ነገሮች ተካረዋል። በአካባቢው ያሉ የሀገር ሽማግሌዎችን ምክርና ሽምግልና አልቀበልም ብሎ በፋኖ አርሶአደር ገበሬዎች ላይ ተኩስ ለመክፈት በከበባና በዝግጅት ላይ ናቸው።
ይህ ወቅት የክፉው ኮሮና በሽታ ወረርሽኝ ወቅት ቢሆንም መንግስት ሆን ብሎ ህዝባችንን በበሽታ ለመጨረስ ያሴረው ሴራ ስለሆነ ሁሉም አማራ በያለበት ሆኖ ትግሉን እንዲያቀጣጥል አሁን ከፋኖ አርበኞች አስቸኳይ ጥሪ ተላልፏል።

አማራ ተነስ ከዳግም ባርነት አምልጥ

Check Also

ሻለቃ ውብ አንተን ስሙት።

በአሜሪካን ሀገር የምትኖሩ የአማራ ማህበራትና የአማራ ልጆች የት ነው ያላችሁት?? Share!

One comment

  1. በሁሉም አቅጣጫ ያለህ አማራ ስማ ስማ‼

    የፀረ አማራው ኦነጋዊ የአብይ አህመድ መንግስት ቅልብ የኦሮሞ ልዩ ኃይልና የኦነግ ወታደሮችን ልኮ በአማራ ፋኖ ላይ በይፋ ጦርነት ከፍቷል።ጦርነቱ በጎጃም አማራ ፋኖዎች በፍኖተሰላም ከተማ አቅራቢያ ትላንት የተጀመረ ዛሬም ተጨማሪ የመከላከያ ወታደር መጥቶ ተራግፏል ነገሮች ተካረዋል። በአካባቢው ያሉ የሀገር ሽማግሌዎችን ምክርና ሽምግልና አልቀበልም ብሎ በፋኖ አርሶአደር ገበሬዎች ላይ ተኩስ ለመክፈት በከበባና በዝግጅት ላይ ናቸው።
    ይህ ወቅት የክፉው ኮሮና በሽታ ወረርሽኝ ወቅት ቢሆንም መንግስት ሆን ብሎ ህዝባችንን በበሽታ ለመጨረስ ያሴረው ሴራ ስለሆነ ሁሉም አማራ በያለበት ሆኖ ትግሉን እንዲያቀጣጥል አሁን ከፋኖ አርበኞች አስቸኳይ ጥሪ ተላልፏል።

    አማራ ተነስ ከዳግም ባርነት አምልጥ‼‼

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.