Breaking News
Home / Amharic / በአርሲ ሀገረ ስብከት በኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ዘግናኝ፣ አረመኔያዊ እና ቃላት ሊገልጹት የማይችሉት የጅምላ ጭፍጨፋ

በአርሲ ሀገረ ስብከት በኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ዘግናኝ፣ አረመኔያዊ እና ቃላት ሊገልጹት የማይችሉት የጅምላ ጭፍጨፋ

በአርሲ ሀገረ ስብከት በኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ዘግናኝ፣ አረመኔያዊ እና ቃላት ሊገልጹት የማይችሉት የጅምላ ጭፍጨፋ መላውን የሰው ልጅ ህሊና በእጅጉ ያሳዘነና ያስቆጣ ድርጊት ነው።
​ይህንን ታላቅ ሀዘን በቁጭት እና ፍትህ በመጠየቅ ጥሪያችነን ለሚመለከታቸው የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን እና አለም አቀፉን ማህበረሰብ መንግስትን ጭምር እንጠይቃለን ።
​ይህ የፍትህ ጥሪ በአርሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸመው አረመኔያዊ ጭፍጨፋ ይቁም ! ተጠያቂዎች ለህግ ይቅረቡ!
​በኢትዮጵያ፣ በአርሲ ዞን በንጹሃን የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ የተፈጸመውና ሰብአዊነት የጎደለው አሰቃቂ የጅምላ ጭፍጨፋ ቃላት ሊገልጹት ከሚችሉት በላይ የሆነ ግፍ ነው። ከ100 ዓመታት በላይ ያስቆጠረው ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናት ሲቃጠል የእምነቱ ተከታዮችና ንጹሃን ዜጎች በማንነታቸውና በእምነታቸው ምክንያት ብቻ በአረመኔዎች በስለት ተቆራርጠው ሲጣሉ መመልከት የሰው ልጅ ህሊና ሊሸከመው የማይችለው ከባድ ሀዘን ነው።
​ዛሬ አርሲ በንጹሃን ደም ጨቅይታለች፤ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጥቁር ለብሳ ወደ ፈጣሪዋ የምታለቅስበትና ፍትህ የምትማጸንበት የታሪክ ጥቁር ጠባሳ ላይ እንገኛለን። ነገር ግን ይህ አልቃሽ የሌለው መጽናኛ ያጣ ሀዘን በመግለጫዎች ብቻ ተሸፍኖ ሊቀር አይገባም።

​የመንግስት ዋነኛ እና ቀዳሚ ኃላፊነት የዜጎቹን ደህንነት መጠበቅና የመኖር መብታቸውን ማረጋገጥ ቢሆንም በየአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛና አረመኔ ኃይሎች በንፁሃን ላይ እንዲህ አይነት ዘግናኝ ጭፍጨፋ ሲፈጽሙ መንግስት ዜጎቹን ከሞት መታደግ አለመቻሉ ታሪካዊና ትውልዳዊ ተጠያቂነትን ያስከትላል።
በሌላ በኩል ደግሞ የቤተክርስቲያኗ መሪዎችና ቅዱስ ሲኖዶስ ከውግዘትና ከመግለጫ ባለፈ ለምዕመናን መፅናኛ የሚሆን ደህንነታቸውን የሚያስጠብቅና ድምጻቸውን በይፋ የሚያስተጋባ ጠንካራና ተግባራዊ እርምጃ ሊወስዱ ይገባል።
ለተፈናቀሉ ዜጎች አስቸኳይ እርዳታ መላክ አለበት ።

​ወደ መላው ዓለም የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች የሚቀርብ የፍትህ ጥሪ
​በመላው ዓለም የምትገኙ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ዓለም አቀፍ ተቋማት የሲቪል ማህበረሰባት እና ፍትህን የምትወዱ የሰው ልጆች ሁሉ! በኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳውያን ላይ እየተፈጸመ ያለው ስልታዊ ጥቃትና ማፃዳት የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት ይሻል። የሰው ልጅ የመኖር መብት በሃይማኖቱና በማንነቱ ምክንያት ብቻ እንዲህ በጭካኔ ሲቀጠፍ ዝምታን መምረጥ ለግፈኞቹ ተባባሪ መሆን ነው።
​ስለሆነም ሁላችንም በአንድ ድምፅ በመነሳት የሚከተሉትን ጥያቄዎች እንድናስተጋባ ጥሪያችንን እናቀርባለን
ለአጥፊዎች ተጠያቂነት ይህንን ዘግናኝ ጭፍጨፋ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የመሩ ያስተባበሩና የፈጸሙ ኦርቶዶክስ ጠል አረመኔዎች በአስቸኳይ ተለይተው ለህግ እንዲቀርቡና ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ።
የመንግስት ኃላፊነት ነው ። የኢትዮጵያ መንግስት ዜጎቹን የመጠበቅ ህገ መንግስታዊ ግዴታውን እንዲወጣ አበክረን እንጠይቃለን ።

የተፈናቀሉትን መደገፍ እና የመልሶ ማቋቋምን በተመለከተ የፌዴራል እና የክልል የአደጋ ስጋት አመራር አካላት በጥቃቱ ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎችን በጊዜያዊ መጠለያዎች
በማገዝ አስቸኳይ ሰብአዊ እርዳታ ምግብ እና አልባሳት እንዲያቀርቡ ጥሪያችነን እናስተላልፋለን ።

ውድ ኦርቶዶክሳውያን የተሰማንን ጥልቅ ሀዘንና ቁጭት ወደ በጎ ነገር ለፍትህ መቆምና ለወገኖቻችን መድረስ የሚሆንበትን ብርታት ለሁላችንም ይስጠን።
አሜን ። አለባቸው ።ሳለኝ አበሻ (ለንደን)

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.