Breaking News
Home / Amharic / ሃይማኖታዊ ጭቆና በኢትዮጵያ

ሃይማኖታዊ ጭቆና በኢትዮጵያ

ሃይማኖታዊ ጭቆና በኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ከሚፈጸሙ ስልታዊና መዋቅራዊ ጥቃቶች መካከል አንዱ ልጆችዋን ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ፌዴራል ድረስ ከሥራ ገበታ፣ከመንግሥት ሥራ፣ከሀላፊነትና ከፖለቲካዊ ተሳትፎ ማግለል ነው።ይኽ ኦርቶዶክስን ያለ ተጠያቂነት ለማጥፋት ታስቦ የሚደረግ መንግሥታዊ ፕሮጄክት ነው። ሥልጣኑን ሙሉ በሙሉ ከተቆጣጠሩት ኦርቶዶክሱ ቢጮህ ሰሚያ አያገኝም።ልክ አሁን እየሆነብን እንዳለው ዓይነት እልቂት ማለት ነው። አገዛዙ ለማድረግ እየተዘጋጀ ያለውን ምርጫን አስመልክቶ በኦሮሚያ ክልል በየቦታው የሚመረጡ የሕዝብ ተወካዮች እጩዎችን ከየትኛው ቤተ እምነት እንደሆኑ በጥቂቱም ቢሆን ለማጣራት ሞክሬአለሁ።እንደ ናሙና የወሰድሁት 27 የምርጫ ጣቢያዎችን ነው።በእነዚህ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የቀረቡት ምርጫ ጣቢያዎች ላይ 108 እጩዎች አሉ።ከእነዚህ መካከል፦
👉ሙስሊም 91 ሰው በፐርሰንት 84.25%ነው
👉 ፕሮቴስታንት 17ሰው በፐርሰንት ሲሰላ 15.75%
👉ኦርቶዶክስ አንድም ሰው የለም
አስቡት፦
👉 ለአምስት ሺ ዘመናት ይኽችን ያገር ያቆያት ኦርቶዶክሱ ነው
👉ዛሬ ሀገሪቱ የምትጠቀማቸው የቱርስት መስዕቦችን ለሀገር ያበረከተው ኦርቶዶክሱ ነው
👉ከፍተኛው የሕዝብ ቁጥር ያለው ኦርቶዶክስ ነው
👉ክፍተኛ ግብር ከፋይ ኦርቶዶክስ ነው
👉ሀገር ተደፈረች ሲባል ሕይወቱን የሚገብረው ኦርቶዶክሱ ነው
👉ለሀገራዊ ልማት ሲባል ከ ፊት የሚሰለፈው ኦርቶዶክሱ ነው
👉ለሀገራዊ መዋጮ ሲሆን ቀድሞ የሚገኘው ኦርቶዶክሱ ነው
✍ የሚገደለውም ፣ የሚሰደደውም ፣እሬሳው በእሳት የሚቃጠለውም፣ከሀገራዊ ተሳትፎ የሚገለለውም፣ሀገር እያለው ሀገር አልባ የሆነውም ኦርቶዶክሱ ነው።በቃን።ከዚህ በላይ ጭቆናን የምንሸከምበት ጀርባ ለንም።ሌላው በሃይማኖት ተደራጅቶ ሥልጣን ይዞ ሲያጸዳን ዝም ጭጭ ብሎ መገዛት ባርነት ነው።ባርነትን መታገስ ደግሞ ከሃይማኖታችንም ከአባቶቻችንም አልተማርንም።በአራቱም አቅጣጫ ያለህ ኦርቶዶክሳዊ ፦
👉ከፍርሃት ቆፈን ተላቀቅ
👉ከማንም ምንም አትጠብቅ
👉 ራስህን ለማዳን ተሰባሰብ
👉 ነገሮችን እንደ አመጣጣቸው ለመመከት ተዘጋጅ።
👉ሃይማኖትና ፖለቲካይለያያል፣ስንሞት እንበዛለን፣እልል በሉ ህንጻ ሠራንላችሁ ወዘተ., እያሉ ከሚያደነዝዙ የዓዉደምህረት ላይ ነጌዶዎችን አትስማ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.