Breaking News
Home / Amharic / እስክንድር ነጋና የታሰሩት የባልደራስ መሪዎች ተፈቱ!!

እስክንድር ነጋና የታሰሩት የባልደራስ መሪዎች ተፈቱ!!

%name ድንገት አመሻሹ ላይ ነው ዕቃችሁን ይዛችሁ ውጡ የተባልነው የባልደራስ አመራርየባልደራስ ከፍተኛ አመራር የሆኑትና በቂሊንጦ ከአቶ እስክንድር ነጋ ጋር ታስረው የነበሩት የፓርቲው የድርጅት ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ቸኮል በዛሬው ዕለት ከምሽቱ 12፡30 አካባቢ የማረሚያ ቤቱ ሠራተኞች ድንገት መጥተው ከማረሚያ ቤቱ እንዲወጡ እንደነገሯቸው አስስረድተዋል።

“ድንገት አመሻሽ ላይ መጥተው ዕቃችሁን ይዛችሁ ውጡ አሉን፤ ያው እቃችንን ይዘን ወጣን። ምንም የምናውቀው ነገር የለም” በማለት አቶ ስንታየሁ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት እንደወጡ በስልክ ለቢቢሲ ተናግረዋል።  አቶ ስንታየሁን በስልክ ባገኘበት ወቅት ከቂሊንጦ ማረሚያ ወጥተው ከአቶ እስክንድር ጋር ከማረሚያ ቤቱ አቅራቢያ ወደሚገኝ ቤተ ክርስቲያን እያመሩ እንደሆነም ገልጸዋል። “በዋናነት የተፈታነው በአምላክ ኃይል ነው፤ እውነት ነው ያሸነፈው፤ የሕዝብ ትግል፣ የሕዝብ እንባ ነው ያሸነፈው” ብለዋል።

Check Also

ኢትዮጵያዉያን የተባበሩት መንግሥታት ስብሰባ ላይ ፈንቅለው ገብተው ተቃውሞ አሰሙ !

Ethiopians protest against Abiy Ahmed in Geneva Switzerland!

መንገዱ በጀግናው ስም ተሰይሟል !

እንባየም ሳላስበዉ ይፈሳል። ብቻ እንደዛሬ ሁኘ አላዉቅም። እግዚአብሔር አምላክ ልቤን አበረታዉ።

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.