Breaking News
Home / Amharic / ባልደራስ ለምርጫ ተወዳዳሪነት በይፋ ተመዘገበ !

ባልደራስ ለምርጫ ተወዳዳሪነት በይፋ ተመዘገበ !

ርጫ ቦርድ ለአራት ፓርቲዎች የእውቅና ሰርተፍኬትና ጊዜያዊ የምዝገባ ፈቃድ ሰጠ

አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአራት ፖለቲካ ፓርቲዎች የእውቅና ሰርተፍኬትና ጊዜያዊ የምዝገባ ፈቃድ መስጠቱን አስታወቀ።

ፓርቲዎቹም ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ፣ አንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ አማራ ጊዮናዊ ንቅናቄ እና እናት ፓርቲ መሆናቸውን ቦርዱ አስታውቋል።

ለፖለቲካ ፓርቲዎች ጊዜያዊ የምዝገባ ሰርተፍኬት ማግኘት የሚቻለው ማመልከቻ፣ በጽሁፍ የምዝገባ ጥያቄ፣ ለሀገር አቀፍ ቢያንስ 200፣ ለክልላዊ ፓርቲ ቢያንስ 100 አመልካቾች የፈረሙበት የስብሰባ ቃለ ጉባኤ ማቅረብ ሲችሉ መሆኑ ተገልጿል።

እንዲሁም የሚመሰረተው የፓለቲካ ፓርቲ ጊዜያዊ ስም ማዘጋጀት ሲችል እና የምርጫ ህጉን እና ተያያዥ ህጎችን የሚያከብር ስለመሆኑ ማረጋገጫ እና ቦርዱ የሚወስነውን የአገልግሎት ክፍያ መፈፀም ሲችል መሆኑ ተጠቁሟል።

ይህ ፍቃድ የሚያገለግለው ለሶስት ወራት ብቻ ሲሆን፥ አመልካቾች በቂ ምክንያት አቅርበው ከጠየቁ ለተጨማሪ 3 ወር ሊራዘም ይችላል ተብሏል።

Check Also

ኢትዮጵያዉያን የተባበሩት መንግሥታት ስብሰባ ላይ ፈንቅለው ገብተው ተቃውሞ አሰሙ !

Ethiopians protest against Abiy Ahmed in Geneva Switzerland!

መንገዱ በጀግናው ስም ተሰይሟል !

እንባየም ሳላስበዉ ይፈሳል። ብቻ እንደዛሬ ሁኘ አላዉቅም። እግዚአብሔር አምላክ ልቤን አበረታዉ።

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.