Breaking News
Home / Amharic / ገንዘባቸው የተወረሳባቸው የአማራና የ አፋር ተወላጆች !

ገንዘባቸው የተወረሳባቸው የአማራና የ አፋር ተወላጆች !

የ35 የአማራ፣ 2 የአፋር ባለሃብቶችና ድርጅቶች የባንክ አካውንት ታገደ

የአማራ ሕዝብ ትግልን ሊደግፉ ይችላሉ በሚል፤ የአማራ ባለሃብቶችን ለማሠርና ንብረታቸውንም ልክ እንደ ትጥቁ ለማስፈታት እንቅስቃሴ መጀመሩን ትናንት በዘ-ሐበሻ ዜና መዘገባችን ይታወቃል።
በኦሮሚያ ብልጽግና ሰዎች የሚመራው የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ዛሬ ለሁሉም ባንኮች በጻፈው ደብዳቤ የ35 የአማራ ባለሃብቶች እንዲሁም 2 የአፋር ባለሃብቶች በባንክ ያላቸው ገንዘብ እንዲታገድ
ለሁሉም ባንኮች የጻፈው ደብዳቤ ዘ-ሐበሻ እጅ ገብቷል። ይህም በኦሮሚያ ብልጽግና እና በአማራ ብልጽግና መካከል ያለውን ሽኩቻ አንዱ ማሳያ ነው ሲሉ የብልጽግና ምንጮች ይናገራሉ። ደብዳቤውን ተመልከቱት፤ ተጨማሪ መረጃዎችን ይዘን እንመጣለን።
በነገራችን ላይ የሞቱ ሰዎችም ጭምር በ እገዳው ስማቸው ተጠቅሷል። 
===============

የአማራ ባለሃብቶችን ማሰር ሊጀመር መሆኑን ምንጮች ለዘ-ሐበሻ ገለጹ:: ብሔራዊ ባንክ ለባለሃብቶቹ ብድር እንዳያራዝም የተከለከለ ሲሆን መክፈል ሲያቅታቸው ንብረታቸውን በሃራጅ ለመሸጥና ሃብቱንወደሌሎች ለማሻገር በሚመስል መልኩ እየተሰራ መሆኑን ምንጮች ተናግረዋል:: እነዚሁ በብሔር አማራ የሆኑ ባለሃብቶች ተመርጠው ዘመቻ የተከፈተባቸው ሲሆን አንዳንዶቹም ቢሯቸው እየተሰበረ ፋይል እንደተወሰደባቸው: የባንክ አካውንቶቻቸው እየታገደባቸው መሆኑ ታውቋል::
 

Check Also

ሻለቃ ውብ አንተን ስሙት።

በአሜሪካን ሀገር የምትኖሩ የአማራ ማህበራትና የአማራ ልጆች የት ነው ያላችሁት?? Share!

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.