Breaking News
Home / Amharic / ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ሲጠቀሙበት የነበረውን የፌስቡክ አካውንታቸውን ….

ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ሲጠቀሙበት የነበረውን የፌስቡክ አካውንታቸውን ….

የአብን ሊቀመንበር የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ሲጠቀሙበት የነበረውን የፌስቡክ አካውንታቸውን ከመጋቢት 2011
ጀምሮ ላለፉት 4 ወራት እየተጠቀሙ አይደለም።

ይህ የሆነው ደግሞ የፌስቡክ አካውንታቸውን አክሰስ ማድረግ ባለመቻላቸው ነው። አዲስ አካውንት ከፍተው መጠቀም
በመጀመሩ በመጀመሪያው ቀንም ድጋሚ መጠቀም እንዳይችሉ ተደርገዋል።
በዚህ የተነሳም ፌስቡክ ጨርሶ እየተጠቀሙ አይደለም።

ይሁንና ለረጅም ዓመታት ሲጠቀሙበት የነበረውን አካውንት የማይታወቁ አካላት እየተገለገሉበት መሆኑን መረዳት ችለናል።
ስለሆነም የንቅናቄያችን አባላት፣ ደጋፊዎችና ሌሎችም ግለሰቦች አካውንቱን ዶክተር ደሳለኝ ሳይሆን ማንነታቸው የማይታወቁ አካላት የሚያስተዳድሩት መሆኑን ተረድታቸው ጥንቃቄ እንድታደርጉ እያስታወቅን በዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ስም በተከፈተ የፌስቡክ
አካውንት የሚተላለፉ መልዕክቶችም የዶክተር ደሳለኝንም ሆነ የአብንን አቋም የማይወክሉ መሆናቸውን ጨምረን እናስታውቃለን።

Check Also

ሻለቃ ውብ አንተን ስሙት።

በአሜሪካን ሀገር የምትኖሩ የአማራ ማህበራትና የአማራ ልጆች የት ነው ያላችሁት?? Share!

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.