Breaking News
Home / Amharic / የጎሳ ፖለቲካ እና ህገመንግስቱ በተቀዳሚ የጎዳው የትግራይን ህዝብ ነው።

የጎሳ ፖለቲካ እና ህገመንግስቱ በተቀዳሚ የጎዳው የትግራይን ህዝብ ነው።

የጎሳ ፖለቲካ እና ህገመንግስቱ በተቀዳሚ የጎዳው የትግራይን ህዝብ ነው።
የትግራይ ህዝብ በንጉሱ ዘመን በሁሉም የኢትዮጵያ ግዛቶች በተለይም ዛሬ አማራ ክልል በሚባለው በዚያን ዘመን ጠቅላይ ግዛቶች ቆይቶም ክፍለሀገራት፤ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ ጉልበት ያለው
በጉልበቱ ተዘዋውረው ሰርተው ሲኖሩ ተከብረውና ተወድሰው እንዲሁም በዜግነታቸው ማግኘት የሚገባቸውን እንደ አካባቢው ማህበረሰብ እኩል እያገኙ ነበር። በደርግ ዘመንም ደግሞ በአገሪቱ ውስጥ
ወደ ተሻለ ለም ቦታ አስፍሮ በግብርና ሙያ ህይዎታቸውን እንዲመሩ መንግስት ድጋፍ ያደርግላቸው ነበር።
ነገር ግን በወያኔ የሚመራው የኢሕአዴግ መንግስት ከተቋቋመ በሗላ፤ ህገመንግስቱ ኮንፈደሬሽን በመሰለ የብሄር ፖለቲካ ስለተቀየረና የፖለቲካ ፓርቲዎች አደረጃጀትም በብሄር በመዋቀራቸው ምክንያት
ለሀገሪቱ አንድነት ስጋት ከመሆኑም በላይ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ተዘዋውረው ሰርተው እንዳይኖሩ አድርጓቸዋል። በተለይም የሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የግብርናውን ስራ ከበድ ስለሚያደርገውና
በቂ የዝናብ ውሃ በአንዳንድ ዘመናትም ስለማይገኝ፤ በዚህ ክፍለሀገር የሚኖሩ የትግራይ ወገኖቻችን በሀገራቸው በኢትዮጵያ ውስጥ ተዘዋውረው ሰርተው እንዲኖሩ አድርጓቸዋል።
ከዚህም በላይ ሁሉም የትግራይ ህዝብ አንድ አይነት ዕርዮት ዓለም እንዳለውና ሁሉም የትግራይ ህዝብ በአንድ አይነት የኢኮኖሚ ስርአት ለመስተዳደር እንደሚፈልግ በማስመሰል፤ የወያኔን የብሄራዊ
ዴሞክራሲን የኤኮኖሚ ስርአት ተቀብሎ ወያኔን መርጧል እየተባለ ከሰላሳ አመት በላይ በስልጣን ላይ ይገኛል።
ስለሆነም እያንዳንዱ የትግራይ ህዝብ እንደ ችሎታው ኑሮውን ሊያሻሽልበት የሚያስችለውን የፖለቲካል ኤኮኖሚ ፕሮግራም ያላቸውን ፓርቲዎች ተገንዝቦ በነጻነት እንዳይመርጥ እድል እንዳያገኝ ሆኗል።
 

Check Also

የኮሎኔል አብይ አህመድ አስገራሚ የትምህርት መረጃዎች ! የትኛው ነው ትክክል?

ሻለቃ ውብ አንተን ስሙት።

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.