Breaking News
Home / Amharic / የአብይ አህመድ ጀሌ ወታደር አልዋጋም እያለ እየሸሸ ነው።

የአብይ አህመድ ጀሌ ወታደር አልዋጋም እያለ እየሸሸ ነው።

ሰበር መረጃ:-

የመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ያለው ወታደር መሳሪያውን እየጣለ በመሸሽ ላይ መሆኑ አንድ ለአንከር ሚድያ ቃለ መጠይቅ የሰጠ የመከላከያ ሰራዊት ወታደር ይህን መስክሯል:: ይህ ከኦሮሞ ብሄር የሆነ የሰራዊቱ አባል እንዳረጋገጠው ወታደሩ የአማራ ህዝብ ጋር ያለውን ጦርነት ለመዋጋት ፈቃደኛ አለመሆኑን ገልጦ ለግዳጅ ሲልኩን “ጁንታውን ልትወጉ ነው” ተብለን ነው የመጣነው ሲል ተናግሯል:: በአማራ የተለያዮ ወረዳዎች ባለፉት ሁለት ሳምንታት በተደረገው ጦርነት ከፍተኛ ሽንፈት የደረሰበት የብርሀኑ ጁላ መከላከያ በመፍረክረክና በመበተን ላይ መሆኑን ይሄው ወታደር አስረድቷል::

በተያያዘ ዜና ከብርጋድየር ጄነራል በላይ ያለ የመከላክያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራር ለአስራ አምስት ቀን ስልጠና በሚል ባስቸኳይ ተጠርተው ከዛሬ ማክሰኞ ጀምሮ ስልጠና መጀመራቸውን አንከር ሚድያ አረጋግጧል:: ለስልጠና የሚገቡ ሰልጣኞች ምንም አይነት ሞባይል ስልክም ሆኔ ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ ይዘው መግባት እንደማይችሉ የተነገራቸው ሲሆን ስብስባው በድንገት የተጠራበት ምክንያት በሰራዊቱ አመራር መካከል የተፈጠረውን ትርምስና መፈረካከስ ለማርገብና በአማራ ክልል በሶስት ወር ይጠናቀቃል የተባለው ዘመቻ ለምን አልተሳካም የሚለውን ለመገምገም እንደሆነ ይገመታል::

ከአንድ ብሄር ብቻ በተመለመሉ ኦነጋዊ አስተሳሰብ ባላቸው ጀነራሎች የተያዘው የመከላክያ አመራር በተራ ወታደሩ ዘንድ የሚሰጠው የግዳጅ ተልእኮ ተቀባይነት እያጣ መምጣቱ የአብይ አህመድ ፋሽስታዊ ቡድንን በጥልቅ እንዳሳሰበውና እንዳስጨነቀው ታውቋል:: ተራው ወታደር በተለይ ኦሮሚኛ ቋንቋ ብቻ የሚናገረው ወደ ወደ ማያውቀው የአማራ መልክዐምድር ሲደርስ ተዋጋ ተብሎ ትዛዥ ሲሰጠው በሚጠበቀው መጠን ለማስፈጸም ስላልቻለ የሚማረከው እየተማረክ የሚሸሸውም እየሸሸ መምጣቱ እነ አብይ አህመድን እያስጨነቃቸው ያለው ዋና ራስ ምታት ሆኗል::

የአማራ ህዝብ ላይጨርስ አይጀምርም:: ህዝቡ ከፋኖዎች ጋር በመቆም ብዙ ወረዳዎችን በቁጥጥር ስር አድርጓል:: ይህ ትግል ከቀን ወደ ቀን እንደ ሰደድ እሳት በመላው አማራ ብሎም ኢትዮጵያ እንደሚስፋፋ ይጠበቃል::

ድል ለአማራ ህዝብ!

Check Also

ሻለቃ ውብ አንተን ስሙት።

በአሜሪካን ሀገር የምትኖሩ የአማራ ማህበራትና የአማራ ልጆች የት ነው ያላችሁት?? Share!

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.