Breaking News
Home / Amharic / የአማራ ሰቆቃ እየቀጠለ ነው:: አብይ አህመድ ስለ አማራ ህዝብ እልቂት እስካሁን ምንም አላለም:: መደመጥ ያለበት !!

የአማራ ሰቆቃ እየቀጠለ ነው:: አብይ አህመድ ስለ አማራ ህዝብ እልቂት እስካሁን ምንም አላለም:: መደመጥ ያለበት !!

ዛሬም ጆሮ የተነፈገው የወለጋ ሰቆቃ!
ኦነግ፣ በመንግሥት አጠራር ሸኔና ኦዴፓ በትብብር አማራን ከበው፣ አንዱ ገዳይ አንዱ አስገዳይ በመሆን በቅንብር እየጨፈጨፉ ነው። ከ 10 000 በላይ የአማራ ህዝብ ተፈናቅሎ ጫካ ገብቶ ድረሱልን ቢል ሰሚ ጆሮ ጠፍቶ ሁሉም ሊያልቁ ነው። ቁስለኛም ሆነ አስከሬን ማንሳት አይቻልም። በጭንቅ ላይ ሆነው ድረሱልን፣ የመንግሥት ያለህ የሚሉትም ሰሚ አጥተዋል። በጣም ያሳዝናል። አብይ አህመድ መንግሥት ሲመሰርት ሰላም ያሰፍናል ስትሉ የነበራችሁ ዛሬስ ምን ትሉ ይሆን? “ፅድቁ ቀርቶ በውጉ በኮነነሽ!” እንዲሉ ሰላሙ ቀርቶብን ህዝብ በጅምላ ከመጨፍጨፍ በታደገም ትልቅ ነገር ነበር።
ሞቱና የጣር ድምፁ የሚሰማው ድርጅትም ይሁን መሪ ያጣ ህዝብ …😭😭😭
…በምዕራብ ወለጋ ዐማሮች እና አማርኛ ተናጋሪዎችን ጥይት ላለማባከን ተብሎ በጅምላ የሚገደሉበትን መንገድ ለሚሰማው ራሱ እረፍት ይነሣል። ይሄን ጭካኔ ሰይጣን ራሱ የሚያወቀው አይመስልም። ከምር ጤናም ያቃውሳል። እኔማ ዛሬስ ከምር አመመኝ። ቀኑን ሙሉ ስወራጭ ዋልኩ። ደወልኩላቸው። አወራኋቸውም። የሚያወሩት ሁሉ ይዘገንናል። የት እና ለመሰን ልተንፍሰው?
• እግዚአብሔር ይድረስላችሁ ወገኖቼ። ኡፍፍፍፍ…

Check Also

ሻለቃ ውብ አንተን ስሙት።

በአሜሪካን ሀገር የምትኖሩ የአማራ ማህበራትና የአማራ ልጆች የት ነው ያላችሁት?? Share!

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.