Breaking News
Home / Amharic / ከግዞት እስር ቤት የተላከ!!

ከግዞት እስር ቤት የተላከ!!

ከግዞት እስር ቤት የተላከ!!
ለኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስትር
አዲስ አበባ

ጉዳዩ:- የሰብአዊ መብቶች ጥሰትን ይመለከታል
እኛ ስማችን ከዚህ ማመልከቻ ጋር አባሪ የተደረገው ቁጥራችን 34 የሆንን አማሮች በሕዝባችን ላይ የማያባራ ሁኔታ የሚፈፀመውን ማንነት ተኮር ጭፍጨፋ የዘር ማፅዳት የዘር ፍጅት ግድያና ጅምላ ማፈናቀል እንዲሁም መንግሥታዊ አቅሞችን በመጠቀም ጭምር የሚፈፀሙ ዘር ተኮር መዋቅራዊና ሥርአታዊ ሁሉን አቀፍ ጥቃቶችን በመቃወማችን የሕግ የሞራልና የተፈጥሮ ኃላፊነታችንን በመወጣታችንምክንያት ተደራራቢ የሆኑ ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች እየተፈፀመብን ይገኛል::
፩: ያለምንም ወንጀል አማራነታችን እንደወንጀል ተቆጥሮ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ሕግን ባልተከተለ መንገድ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ታፍነን በጅምላ ታግተን እንገኛለን::
፪: በፀጥታ ኃይሎች እገታ በተፈፀመብን ወቅት ከፍተኛ ድብደባ አማራነታችን እየተጠቀሰ አዋራጅ ዘለፋ ስድብና ዛቻ ተፈጽሞብናል::
፫: በፌድራል ወንጀል ምርመራ ቢሮ ከታገትንበት ጊዜ ጀምሮ ብሔር ተኮር ዘለፋ ማስፈራራት የግድያ ዛቻ እንዲሁም በጨለማ ክፍል ማሰርን ጨምሮ ቤተሰብ ማንገላታትና ዛቻ የዕለት ተዕለት ሰቆቃ ሆነውብናል::
ከዚህ በከፋ መልኩ መሳሪያ የታጠቁ የፀጥታ ኃይሎች በሕይዎት የመኖር መብታችንን ለመንጠቅ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ የከፋ ተጋላጭ አድርጎናል::
፬: ፍርድ ቤት የመቅረብ የሕግ ጠበቃ የማማከር የሃይማኖት አባት የማግኘት እንዲሁም በቤተሰብና ጎብኝዎች የመጠየቅ ሰብአዊ መብቶቻችን ሙሉ በሙሉ ተገድበው ይገኛሉ::
በመሆኑም የፍትህ ሚኒስቴር ከላይ በዝርዝር ያስቀመጥናቸውን እጅግ አስከፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ባስቸኳይ ማስተካከያ እንዲደረግባቸው በሕግ የተጣለበትን ኃላፊነት እንዲወጣ እየጠየቅን ይህ አቤቱታ በግልባጭ የተደረገላችሁ ሀገራዊ አህጉራዊና አለማቀፋዊተቁአማት የኢትዮጵያ መንግሥት አለማቀፍ የሰብአዊ መብት መርሆችን አክብሮ እንዲንቀሳቀስና በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈፅመውን ማንነት ተኮር ጥቃት እና ጭፍጨፋ እንዲያቆም ታሪካዊ ኃላፊነታችሁንትወጡ ዘንድ እንጠይቃለን::
ከሠላምታ ጋር
የማይነበብ ፊርማ 

https://www.facebook.com/photo/?fbid=10232692467993761&set=a.3786642424260
 

Check Also

ሻለቃ ውብ አንተን ስሙት።

በአሜሪካን ሀገር የምትኖሩ የአማራ ማህበራትና የአማራ ልጆች የት ነው ያላችሁት?? Share!

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.