Breaking News
Home / Amharic / ብፅዑ አቡነ አብርሃም መግለጫ ሰጥተዋል !

ብፅዑ አቡነ አብርሃም መግለጫ ሰጥተዋል !

በመግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች

፩. ቤተ ክርስቲያን የራሷ ነፃነት አላት

፪. ያም ይኽንን አድርጊ ይሄም ይኽንን አድርጊ ስላላት እየተጎች የተባለችውን የምታስተናግድ አትኾንም አይደለችምም።

፫. ማንም ይኽን አድርጊ እያለ ሊጎትታት አይችልም። ነገር ይኽንን በሉ ይኽንን ካላደረጋችሁ የሚባል መያዣ ነገር ቤተ ክርስቲያን አስተናግዳም አታውቅም። ወደፊትም አታስተናግድም። ወደፊትም የመጣውን በጸጋ ከምትቀበል ውጭ። ይኽንን አድርጊ ስልሽ ብቻ ነው የምታደርጊው የሚለው አስተሳሰብ ጨርሶ የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ይነካል።

፬. መንግሥት በዓለ ጥምቀትን ለማክበር ቅድመ ኹኔታ ማስቀመጡን የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ በመግለጫቸው ጠቁመዋል። [የአቡነ ቄርሎስን እና የአቡነ ሉቃስን] አቋም በበዓሉ እንድታወግዝ መንግሥት አቋም ይዟል።

፭. መንግሥት አኩራፊ ሊኾን አይገባውም። ይኼንን ካላልሽ እንዲህ አላደርግም ማለት አይገባም።

፮. ሱሪ በአንገት አውጣው የሚባል ነገር ቤተ ክርስቲያን አትሸከምም

፯. መኪና ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ሲገባ የማይፈትሹ ሲወጣ የሚፈትሹ የመንግሥት ጥበቃዎች አሉ። የሚገባ መኪና አይፈተሽም የሚወጣ መኪና ይፈተሻል። ምንድን ነው የተፈለገው? ከቤተ ክርስቲያንስ ምንድን ነው የሚወጣው? መድፍ ነው? መሣሪያ ነው?

እኛ መሪዎቹ የማናውቀው ፈታሽ አቁሞ መፈተሽ ድፍረት ነው። የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕልውና መፈታተን ነው።

፰. መደፋፈሩ በዝቷል። መንግሥት ቤተ ክርስቲያኒቱን ደፍሯታል። አልፎ ይሔዳል። ቤተ ክርስቲያንን መድፈር አደጋ ነው። ለሃይማኖቱ የማይሞት የለም።

አዛዣችን በዝቷል። ላዘዘን ኹሉ አጎንብሰን እንችላለን እንዴ? ሃይማኖታችን ከሚፈቅደው ውጭ። በሉ የተባልነውን ኹሉ ማለት እንችላለን እንዴ? ለእኔ አድርግ የሚለኝ ሃይማኖቴ ብቻ ነው። ማስፈራሪያ አይገዛንም። ዘጠኝ ሞት መጣ ቢሉት አንዱን ግባ በለው።

፱. በየሔድንበት በየቢሮው ደሞ ለኦርቶዶክስ? እየተባልን ነው። ቢያንስ አይኾንም እንኳ [የአባት ነው] አትቁም ያሉት ለማኝ አትቁም ነው። ያንን ያንን ያርሙ።

እዚህ እኛው ቤት አድር ብዬው ቅጥረኛው ስለሚበዛ ነው። የድፍረት ኃጢአት በዝቷል። ድፍረት የቤቱን ሰው ገዝቷል የውጭውንም ሰው ገዝቷል። የማትደፈረውንም ቤተ ክርስቲያን እያስደፈረ ይመጣል። አኹን የቀረው በሉ ውጡ ብሎ የመረካከብ ሥራ ነው ይኽች ቤተ ክርስቲያን የቀራት። ይኽንን ደግሞ ቆሞ የሚያይ የለም።

የጎጠኝነቱ ምንጩ ቤተ ክህነቱ ኾኗል። ከሃይማኖቴ ቋንቋዬ ይበልጣል የሚሉ ሰዎች የተነሡበት ጊዜ ነው። ስወለድ ቋንቋዬን ይዤ ነው የተወለድኹት ሃይማኖት በኋላ ነው የመጣ ነው የሚሉ ካህናት የተፈጠሩበት ወቅት ነው።

፲. ከሃይማኖቴ ጋር የእኔ ነፍስ ትወጣለች። በሃይማኖት አንደራደርም።

አንበርክኬ ልግዛ የሚለው ይቁም

ለመጨረሻው ጸዋት ወ መከራ ራሳችንን እናዘጋጅ!

Check Also

የኮሎኔል አብይ አህመድ አስገራሚ የትምህርት መረጃዎች ! የትኛው ነው ትክክል?

ሻለቃ ውብ አንተን ስሙት።

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.