Breaking News
Home / Amharic / በቡራዩ ከተማ በተፈፀመ ጥቃት የከተማው ፖሊስ አዛዥ ኮሚሽነር በጥይት ተገደሉ።

በቡራዩ ከተማ በተፈፀመ ጥቃት የከተማው ፖሊስ አዛዥ ኮሚሽነር በጥይት ተገደሉ።

አሥራት:_ የካቲት 13/2012 ዓ/ም

ዛሬ የካቲት 13/2012 ዓ/ም በቡራዩ ከተማ በተፈፀመ ጥቃት የከተማው ፖሊስ አዛዥ ኮሚሽነር ሰለሞን ታደሰ በጥይት መገደላቸው ታውቋል። ከኮሚሽነር ሰለሞን ጋር የነበሩ የአዲስ አበባ ዙሪያ ልዩ ዞን የልዩ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ተስፋዬ ድንቁም በጥይት ተመተው የቆሰሉ ሲሆን ወደ ሆስፒታል ተወስደው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ተብሏል።

ጥቃት የተፈፀመው ከቀኑ 6 ሰዓት አካባቢ ሲሆን ሁለቱ የፀጥታ ኃላፊዎች አብረው ምሳ በመብላት ላይ እንደነበሩ ተገልፆአል። ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ከመንግስት ጥቃቱን እና ጥቃት ፈፃሚውን በተመለከተ የተሰጠ መረጃም ሆነ ማብራርያ የለም።

ከሰሞኑ (ትናንት በሀረር፣ በቅርቡ በጅማ፣ እና ሌሎች አካባቢዎችም) በእነ ጀዋር ሙሀምድና በጠቅላይ ሚኒስትሩ ደጋፊዎች መካከል እርስበርስ ግጭት መፈጠሩ ይታወሳል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኦሮሚያ አካባቢ እየተስተዋለ ያለው አለመረጋጋት አሳሳቢ ደረጃ ላይ የደረሰ ሲሆን ከመሰል በባለስልጣናት ላይ ከሚፈፀሙ የግድያ ወንጀሎች ባሻገር ብሄር እና ሀይማኖት ተኮር ጥቃቶችም የበርካቶችን ህይወት እየቀጠፈ ይገኛል።

በቅርቡም ከተለያዩ በክልሉ ከሚገኙ ዩንቨርስቲዎች ከ35 ሺህ በላይ የአማራ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ለማቋረጥ የተገደዱ ሲሆን በተያያዘም ከደምቢ ዶሎ ዩንቨርስቲ ህይዎታቸውን ለማትረፍ ወደ ወደ ቤተሰቦቻቸው በመመለስ ላይ የነበሩ ተማሪዎች በወለጋ አካባቢ ታግተው እስካሁን ደብዛቸው መጥፋቱ ይታወቃል።

Check Also

ሻለቃ ውብ አንተን ስሙት።

በአሜሪካን ሀገር የምትኖሩ የአማራ ማህበራትና የአማራ ልጆች የት ነው ያላችሁት?? Share!

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.