Breaking News
Home / Amharic / በመከራችንም ሐሴት እናደርጋለን! – ስንታየሁ ቸኮል

በመከራችንም ሐሴት እናደርጋለን! – ስንታየሁ ቸኮል

በመከራችንም ሐሴት እናደርጋለን!

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክርስቲያን ጉዳይ የመጀመሪያ የዐቃቢ ሕግ ተከሳሽ ሆኛለሁ እኔ እንደ በረከት እቆጥረዋለሁ መከራ ትዕግሥትን እንደሚያስገኝ እናውቃለንና።
በእግዚአብሔር ክብር ተስፋ በማድረግ ሐሴት እናደርጋለን። በዚህ ብቻ ሳይሆን በመከራችንም ሐሴት እናደርጋለን ምክንያቱም መከራ ትዕግሥትን እንደሚያስገኝ እናውቃለን።
ትዕግስትም ፤ ጽናትን ፤ ጽናትም የተፈተነ ባሕርይን ፤ የተፈተነ ባሕርይ ተስፋን ፤ ተስፋ ለዕፍረት አይዳርገንም።
ውሃ በማያነሳ በ6 አንድ አይነት የፈጠራ ክስ ከሰዉኛል ዛሬም ፍ/ቤት ከመመላለስ አላረፍኩም በክፋት መንገድ ፈፅሞ የሚሳካ የለም።
ሰዉ በብሄሩ ምክንያት ተለይቶ ለምን ይገደላል ለምን ይፈናቀላል ያለች ነፍስ እውነትን ያነገበች “ቃል” በእውነት ታሸንፋለች። የጊዜ ጉዳይ ነው።

በሀገራችን ብዙ ነገሮች በፍጥነት እየተለዋወጡ ነው አንዳንዱን በትዝብት አልፈን ደካማ ጎኖቻችንን በማረም ወደትግሉ እንመጣለን ቅድሚያ ለልጆቼ ምክር ዕድል እሰጣለሁ
ስለኔ አብዝታችሁ የተጨነቃችሁ በሙሉ ሁሉንም ሰዎች እንዲሁም የሚዲያ ተቋማት የቤተሰቦቼ ጠያቂዎቼን በሙሉ አመሰግናለሁ ጠበቆቻችን አቶ ታለማ ግዛቸው አዲሱ ጌታነህ አመሰግናለሁ ትግሉ ይቀጥል።

Check Also

የኮሎኔል አብይ አህመድ አስገራሚ የትምህርት መረጃዎች ! የትኛው ነው ትክክል?

ሻለቃ ውብ አንተን ስሙት።

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.