Breaking News
Home / Amharic / ሻለቃ ዳዊት ወልደ ጊወርጊስ ማናቸው ? who is Major Dawit W. Giorgis?

ሻለቃ ዳዊት ወልደ ጊወርጊስ ማናቸው ? who is Major Dawit W. Giorgis?

መነበብ ያለበት
በሳልና ጠንከር ያለ መልእክት ለደም ነጋዴወችና ለድል አጥቢያ አርበኞች
በሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊወርጊስ
—–
የአማራ ሕዝባዊ ግንባር የውጭ ድጋፍ ሰጪ ግብረ ሀይልን እዚህ ለማድረስ ቁልፍ ሚና በመጫወቴ ደስተኝ ነኝ:: ይህንን እድል ለሰጠኝ ወደር ለሌለው ጀግና እስክንድር ነጋ ምስጋናዬን እቀርባልሁ:: ይህንን ግዙፍ ሀላፊነት ለመወጣት ከሚታወቀው በላይ ያለ እረፍት ሌት ተቀን የሰሩትን የስራ ባልደረቦቼን እደንቃለሁ:: አመሰግናለሁ::
እኔ የስራ ሰው ነኝ:: የእወቀትም ሰው ነኝ:: ታሪካዊና ትምህርታዊ የሆኑ አራት መፅሀፎችም ፅፌአለሁ:: በእንግሊዝኛም በአማርኛም::አልቀረብኝም:: ቁጥራቸው በጣም ብዙ የሆኑ ምሁራዊ ፅሁፎችን አሳትሜአለሁ::ከአውስትራሊያ አውሮፓና አሚሪካ ካናዳ የተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ለብዙ አመታት ቀርቤአለሁ:: ፅሁፎቼም በ CNN ሳይቀር ወጥተውልኛል::
አገልግሎቴን ግን የምመዝነው በተግባሬ ነው:: እውቀቴን በተግባር በማዋል የተመሰከረልኝ ነኝ:: እውቀትና ተግባርን በማያያዝ በውትድርና ሙያ፣ በኤርትራ አስተዳዳሪነት፣ በዲፕሎማሲ፣ በተባበሩት መንግስታትና ለተለያዪ መንግስታት በችሎታ አማካሪ ሆኜ አገልግያለሁ::
ሰውም የሚያውቀኝ : እኔም እራሴን የማውቀው እንደ ተግባር ሰው ነው::እውቀቴን ለተግባሬ መሳሪያ እድርጌ የኖርኩ ከጦርሜዳ እስክ ህይወት ማዳን ታላላቅ ዘመቻዎች (humanitarian operations) በእውቀትና በኩራት ያገለግልኩ ነኝ:: ለኢትዮጵያ አንድነትና ለአገሬ ህዝብ ፍቅሬን በደሜ አስመክሬአለሁ:: በውጊያ ቆስያለሁ:: አድር ባይ ሆኜ በደርግ የፖለቲካ ሥርዓት መቆየት ስችል ከሥርዓቱ መራቅ ብቻ ሳይሆን ወጥቼ ስርአቱን ለማስለወጥ ረዥምና ውስብስብ ትግል ውስጥ የነበርኩ ነኝ:: ለዚሁ ትግል በሱዳንና በኬንያ ጠረፎች አድርገን አንዳንድ ሁኔታዎችን ለማስተባበር አገር ቤት በድብቅ በእግር ገብቻለሁ:: በጊዜው እድሜዬም ትንሽ አልነበረም::
ደርግ ስሜን ለማጥፋት ያደረገውን ዘመቻ በህግ ሀሰት መሆኑን እስመስክሬአለሁ::
በአንድ ህይወት ይህንን ያህል የሥራ ውጤት ያካበተ ብዙም ሰው አይገኝምብል ማጋነን አይሆንብኝም። ለዚህም እግዚአብሄርን ከማመስገን አላቋርጥም::ለእዚህ ነው የመጨረሻውን መፅሀፌን “What a Life” ያልኩት:: ብዙ ድካምና ጊዜ የወሰደ መፅሀፍ ነው:: የሶስቱም መፅሀፎች ሽያጭ ለበጎ ስራ የተሰጡ ናቸው:: ማሳተሚያውን በግሌ ነው የከፈልኩት:: የመጨረሻው ግን በአስተዋፅኦ ነው የተከፈለው::
አማራ ሲጎዳ፣ የዘር ማጥፋት ወንጀል ሲፈፅምበት ከጎኑ ቆሜአለሁኝ:: አብይንና የወንጀሉ እስፈፃሚዎችን በኢንተርናሽናል ፍርድ ቤት ለማቅረብ ሌሎች ስራዎቼን እቁሜ ለሁለት አመት በጎደኞቼ ድጋፍ ጥናቱን አጠናቀን ለፍርድ ቤት አቅርበናል:: የኢንተርናሽናል ፖለቲካ መሰናክል እጋጥሞን አብይ አህመድ ፍርድ ቤት ገና አልቀረበም:: ከዚያም በሁዋላ ብዙ ወንጀሎች ስለ ተፈፅሙ ተጭማሪ ስራዋች ይጠይቃል:: በጊዜው ከነበረችው የፍርድ ቤቱ አቃቤ ሕግ ( ICC prosecutor general) ጋር ለዚህ ጉዳይ በቀጥታ የተገናኘ ሌላ ኢትዮጵያዊ አላውቅም:: ከእኔ ጋር በቀጥታ ተፃፅፈናል:: በእሷ ሥር ከነበሩ የህግ አዋቂዋችና የክፍል ሃላፊዋች ጋር ክሱን በተመለከተ ፕሮፌሽናል ውይይት እድርገናል:: ጥናቱም ሆነ ለዚህ ጥረት ተብሎ የተሰበሰበው ገንዘብ በቤተ ክህነቱ አካውንት ይገኛል::
ዛሬም ከእስክንድር ሌላ ጥሪ ሲመጣብኝ ስራዬን ሙሉ ለሙሉ አቁሜ ተቀላቅየዋለሁኝ:: ራሴን ጡረታ ካስወጣሁ በሁዋላ The Africa Institute for Strategic and Security Studies (AISSS) www. http://aisss.org አፍሪካ ምድር አቋቁሜ የድርጅቱ ዋና ስራ እስኪያጅ ሆኜ በመስራት ያለሁበትን ትቼ አለክፍያ ሙሉ ለሙሉ ጊዜዬን ለፋኖ ትግል ስጥቻለሁ:: የፋኖ እንቅስቃሴ ከተጀመረ በሁዋላ በአለም ደረጃ ትግላችን እንዲታወቅ የተደረገው ከግንባሩ ምስረታ በሁዋላ ነው::በኢንትርሽናል ደረጃ በአውሮፖና በአሜሪካ በአፍሪካ ( በዲፕሎማሲ ዘርፍ) በይፋ ከተነገሩት ሌላ በግንባሩ ስም እኔ የፈፅምኳቸው ጊዜው ሲደርስ ይገለፃሉ::
በአስራ ስባት አመቴ ወታደርነት የታጨሁ: ሶስት አመት ከታወቀው የቀኃስ ወታደራዊ አካዳሚ የሰለጠንኩ: አንድ አመት አሜሪካን አገር 10 ወር ሌላም ቦታ ለጥቂት ወራት ተጨማሪ ልዩ ስልጠና የፈፅምኩ ኩሩ ወታደር ነኝ:: አራት አመት ቀኃስ ዪኒቨርስቲ: (LLB) ከዚያ ሁለት ዓመት ኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ ( JD – Doctor of Jurisprudence) ቀጥሎ SMU ቴክሳስ ለPhD ቆይቼ የእናት አገር ጥሪን ተቀብዬ በደርግ ጊዜ አገሬ ተመልሻለሁ::ከዚህም በላይ በሶስት ታላላቅ ዩኒቨርሲቲዋች ( Princeton, Universty of Cape Town,Boston University, African Studies Center) በተለያዩ ጊዚያት Visting Scholar ሆኜ ተስይሜ ምርምር ስራዎች ውስጥ ተሳትፌአለሁኝ::
እንደ ዛሬው ሳይሆን በቀድሞ አባቶቻችን አርበኝነት ስሜትና ሥነስርአት ተኮትኩቼ እዚህ የደረስኩ: የዘመኑ ትምህርትና ምቾት ያልለወጠኝ ኩሩ ልበ ሙሉ ኢትዯጵያዊ ነኝ:: የእኔ አማራነት፣ የእኔ እስተዋፅኦ፣ የእኔ ኢትዮጵያዊነት በጥቂት የሴራ ፓለቲከኞች፣ ቡድንተኞችና ምቀኞች የሚተች አይደለም:: በጠባብ እውቀት: እዚህ ግባ በማይባል ልምድ: ወይንም አለምንም ልምድ: ድንበር በዘለለ ምቀኝነት: የእኔን ምንነትና ማንነት ማንቋሸሽ ጊዜው እልፎአል:: ህይወቴ ሲፈተሽ ኖሮአል:: ምክትል ሚኒስትር፣ በሚኒስትር ደረጃ ኮሚሽነር፣ የኤርትራ ክፍለሀገር ዋና ተጠሪ የነበርኩ፤ ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት በሁዋላ ያልታየ ታላቅ ኢንተርናሽናል የረሀብ ዘመቻ የመራሁ፣ በብዙ አለም አቀፍ ፅሁፎችና መድረኮች የተጠቀስኩ፣ ከብዙ መንግስታት መሪዋች ጋር በልኡካን መሪነት ቀጥሎም ከ25 ዓመት በላይ በኢንተርናሽናል አማካሪነት አፍሪካ የስራሁ፣ ለመሪዎች ጥናት ያቀረብኩ፣ ከታላላቅ ስዎች ጋር የተወያየሁ፣ ብዙ የተመስገንኩና የተከበርኩ ሰው ነኝ::
አማራን ለማደራጀትና ማህበራቱ በአንድ ጃንጥላ ስር ሆነው እንዲታገሉ የዛሬ ስምንት ዓመትና ከዚያም በሁዋላ ከቅርብ የትግል ወዳጆቼ ጋር ( አቶ ሃይለ ገብርኤል እስረስና ፕሮፌስር ጌታቸው በጋሻው) ብዙ እልህ አስጨራሽ ስብስባዎች መርቻለሁ:: በመጨረሻም “አንድ አማራ” የሚለውን ድርጅት አዋልደናል:: አብይ ስልጣን ላይ ሲወጣ ድርጅቱ ከሰመ:: አሁን ያለው “አንድ አማራ” ከቀድሞው ጋር የተያያዘ አይደለም::
ታሪኬን ብትጠመዝዙት፣ ያልኩትን ያላልኩትን እንደሚመች እየተረጎማችሁ ለራሳችሁ ቦታ ለማመቻቸት የምትፈልጉ ሁሉ በራሳችሁ ችሎታና መስዋእትነት ተፈረጁ እንጂ በእኔ ትከሻ ላይ ለመረማመድ እትሞክሩ:: ስለእኔ ምስክርነት የተፃፈውን፣ የተነገርውን፣ ወይም ጠቅላላ አስተዋፅኦዬን በቅርብ እያወቁ የማይናገሩ ብዙዎች ናቸው:: እኔን ማመስገን እነሱን ማሳነስ ይመስላቸዋልና:: የማያውቁት ደግሞ እንደትናንት ጎደኞቻቸው ስለሚያዩኝ እንደፈለጉ ያብጠለጥሉኛል:: ለእድሜ እንኳን ክብር የላቸውም:: ለማወቅም ለመጠየቅም አይሞክሩም:: ከእናንተ ጋር እልተወዳደርኩም:: ልምዳችን፣ እውቀታችን፣ አስተዋኦዋችን፣ ስነስርአታችን በጣም የተራራቀ ነው:: በጡረታ ጊዜ ጥሪ ተቀብዬ የመጣሁ ነኝ:: ጊዜዬ ውስን ነው:: እግዜር ቀናውን መንገድ ያሳያችሁ::
ባለቀ ሳዓት እስክንድርና ድርጅቱን ለማፍረስ ስሙንም ለማጠልሽት የሚካሄደው ዘመቻ አለምክንያት አይደለም:: ከጀርባው ሌላ ተንኮል ከሌለው በስተቀር በቅንነት የተነገረ ትችት ነው ብሎ ለመረዳት አስቸጋሪ ነው:: ዛሬ አማራው ድል አፋፍ ባለበት ወቅት እስክንድር ለፋኖ አስተባባሪነት አይመጥንም ማለት አማራ ነኝ የሚል ሁሉ ሊያወግዘው ይገባል:: ድል አፋፍ ያደረስን አንድነታችን ነው:: ጠላት ሊያጠቃ የሚፈልገው ይህንን ጥንካሬአችንን ነው:: ስንት ተፃፈ? ለዘመናት ስንት ውይይት ተደረገ? የስንት ሰው ህይወት ተፈተሽ? ከዚያ ዘመን በሁዋላ ዛሬ ፋኖ ወደወሳኙ የትግል ምእራፍ ሲያሽጋግረን ተናጋሪዎች፣ ፀሀፊዎች፣ አንደበታቸውንና እውቀታቸውን ከሜዳ ትግል ጋር ማገናኘት ባቃታቸው ወቅት: ብቅ ያለው እስክንድር ብቻ ነው:: እኛ ነን የበለጠ የምንመጥነው ካሉ ከሞቀ የአሜሪካ መኖሪያቸውና ቤታቸው ወጥተው ለምንድነው በረሀ እንደእስክንድር የማይገቡት? እስክንድር ቦታውን ይለቅላቸዋል። ተራ ፋኖ ሆኖ ያገለግላል:: አንመጥናለን የሚሉ ሁሉ ይውጡ!
ይዝመቱ!! ወይም አርፈው ይቀመጡ:: በስንት መከራ የተገኘውን እንድነት አይከፋፍሉ::ምን ዓይነት እውቀትና አመለካከት ነው በእስክንድር የሚያስቀና? ማን ነው ከዲያስፓራ መካከል እስክንድር ጫፍ የሚደርስ? በውጭም በውስጥም ትግሉን አስተዋውቆና አስተባብሮ መሸጋገሪያው ሊያደርስን የሚችል የመሪነት፣ የአስተባባሪነት ምግባርና ተአማኒነት ያለው ባለንበት ወቅት እስክንድር ብቻ ነው:: መአድ ሲመሠረት እስክንድር መስራች አባል ነበር.:: ከዚያም በፊት ሆነ በሁዋላ የተመዘገበ ታሪኩ እንድሚያሳየው እስክንድር ለአማራ ትግል መስዋእትነት ሲከፍል የቆየው የዛሬ ተቺዎች የትግል ሜዳ ላይ ፈጽሞ ባልነበሩበት ጊዜ ነው።
ዛሬ ፋኖ የብአዲንን መዋቅር በጣጥሶና የፋሽስቱ የኦሮሙማንና አውዳሚ ሃይል ደቁሶ ወደ አዲስ አበባ እየተቃረበ ሲሄድ ስልጣን የሸተታቸው ሁሉ ከየጓዳቸው በመውጣት የአማራን የህልውና ትግል ለመጥለፍና ለማደናቀፍ ብዙ የድል አጥቢያ አርበኞች አሰፍስፋችኋል። ትእግሥት ይኑራችሁ! በሚገነባው አዲስ የፖለቲካ ሥርአት ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስለሚኖር ስልጣን ፈላጊዎች ዕድላችሁን ለመሞከር ለዚያ ጊዜ ተዘጋጁ! እዚያ ለመድረስ ግን ዛሬ በአንድነት መታገል አማራጭ የለውም:: ከሌሎች ጀግና የፋኖ አመራሮች ጋር ሆኖ እዚያ ሊያደርስን የሚችለውን እስክንድር ነጋን ለማስናከል መሞከር ግን ትግሉን አሳልፎ ለጠላት መስጠት ማለት ነው:: ከጠላት ጋር መሰለፍ ማለት ነው።
አሁን ካለንበት ተነስተን ታላቁ ግባችን ላይ ያተኮረ ሥራ ለመሥራት ሙያ፣ እውቀት፣ ቅንነት፣ ትክክለኛ የፖለቲካ አቋም ያላቸው ታጋዮችን በየዘርፋ በአስቸኳይ ማሰማራት ለወሳኙ የትግል ምእራፍ አማራጭ የለውም:: ከዚህ ወዲያ ያለው ትግል ሙሉ ለሙሉ ታላቁ ሰዕል ላይ ማለትም አራት ኪሎ ላይ ያተኮረ መሆን አለበት። ምንም ይሉኝታ፣ ፍርሀት፣ ጥርጣሬ፣ መከፋፈል የሌለበት ቁርጠኛ ትግል መሆን አለበት:: ትኩረታችን በአማራው ላይ የዘር የማጥፋት፣ የማፈናቀል፣ ቤተእምነቶቻችንንና ታሪካዊ ቅርሶቻችንን የማፍረስ ወንጀል በፈጸሙብን ላይ መሆን አለበት። የአማራ እናቶችንና ሴት ልጆችን በደፈሩት ላይ መሆን አለበት። እርስታችንን በማስመለስ ላይ መሆን አለበት። ለዘለቄታው የአማራን ሕልውና በማረጋገጥ ላይ መሆን አለበት። ትኩረታችን ከላይ የተጠቀሱትንና ሌሎች ወንጀሎችን በአማራው ላይ የፈጸሙትንና ያስፈጸሙትን ሁሉ ለፍርድ በማቅረብ ላይ መሆን አለበት። በእነዚህ ዓላማዎችና በፋኖ መሀከል ገብቶ በእዚህ ያለቀ ሰዓት ሌላ ከፋፋይ እጀንዳ የሚያሲይዙ ላይ ጥብቅ ውግዘት መፈፀም አለበት:: በ120 ሚሊዮን ህዝብ ጉዳይ ላይ ጥቂት ግለስቦች ኢምንት ናቸው:: ግን ከኋላቸው እነማን ተስልፈዋል ብሎ መጠየቅም ተገቢ ነው። ሁሉም ለራሱ ሲል ይጣፍጥ:: የፋኖን ቁርጠኛነት ምንም ሀይል አያቆመውም!
ቢሆንም ጥቂቶች የሚያስተናግዱት አጀንዳ ግን በሜዳ ላይ የማያስፈልግ መስዋእትነት ሊያስከፍልና የአማራን ስቆቃ ሊያራዝም እንደሚችል መርሳት የለብንም:: ስለሆነም በአይቀሬው የፋኖ ድል ማግስት እነዚህ የሞት ነጋዴዎች የመጀመሪያ ተጠያቂዎች ይሆናሉ::
ድል ለአማራ ህዝብ !!!
መነሻችን የአማራ ሕልውና!
መድረሻችን የኢትዮጵያ አንድነት!
ሻለቃ ዳዊት ወልደ ጊዮርጊስ

Check Also

የኮሎኔል አብይ አህመድ አስገራሚ የትምህርት መረጃዎች ! የትኛው ነው ትክክል?

ሻለቃ ውብ አንተን ስሙት።

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.