የታገቱት የአማራ ተማሪዎች ስለመለቀቃቸው ማስረጃ የለም።
የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ትላንት ምሽት 4 ሰዓት ወደ ታገቱ ተማሪዎች ወላጆች እንደደወሉና ወላጆችም ስለልጆቻቸው መለቀቅ መረጃ እንደሌላቸው እንደገለፁላቸው በትዊተር ገፃቸው ገልፀዋል! ሊቀመንበሩ ትላንት ምሽት አቶ ንጉሱ ጥላሁን በመንግስት ድርድር ተለቀዋል ያሏቸው ተማሪዎችን ዛሬ በሚዲያዎች እንዲያቀርቧቸው ጠይቀዋል። ዶ/ር ደሳለኝ የታገቱ ተማሪዎች ስምና ፎቶዓቸው አለንም ብለዋል። Via Tikvah-Eth
Read More »