(የህግ እውቀቱ ያላችሁ በቀላሉ ትረዱታላችሁ)
የካፒቴን ማስረሻ የምርመራ መዝገብ ተዘግቶ ነበር፣ ፖሊስ ወደማረሚያ እንድወስድ ፍ/ቤቱ ይፃፍልኝ የሚል ነገር አቅርቦ ፍ/ቤቱ በተዘጋ መዝገብ ይሄንን የማዝዝበት የህግ አግባብ የለም በማለት ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርጓል። በዚህ መሃል ያመጡት ልዩ ሃይሎች ወደየት እንደሚወስዱት ግራ ተጋብተው ለረጂም ሰዓት ፍ/ቤቱ ግቢ ውስጥ አስቀምጠውት ቆይተዋል።
ከዚህ በኋላ የተፈጠረው ያሳፍራል፣ ፖሊስ ጉዳዩን የያዘውን ዳኛ ለፕሬዘዳንቱ ከሰሰ፣ ዳኛው በተራው ለችሎት ተገተረ፣ ሰብሳቢ ዳኛ አቶ ሰውነት ከበደ የእስር ትዕዛዝ እንዲፅፍ ዳኛውን አዘዘ፣ ዳኛውም የታዘዘውን አደረገ። አሁን መልሰው ወደማረሚያ ወስደውታል።
ፍትህ ሲረገጥ በ ዓይኔ አየሁ።