ፓርላማው የኦሮሚያ ክልል ፍርድ ቤቶች በአዲስ አበባ የዳኝነት ስልጣን እንዲኖራቸው የሚፈቅድ ሕግ አጸደቀ።
በቀዳማዊ ኃይለስላሴ ዘመነመንግስት ጸድቆ ላለፉት 64 ዓመታት በሥራ ላይ የቆየው የወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአት ተሻሽሎ ፀድቋል።
ሕጉ የማስረጃ ሕግ ተካቶበት ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የፀደቀ ሲሆን፤ የኦሮሚያ ክልል ፍርድ ቤቶች
በአዲስ አበባ የዳኝነት ስልጣን እንዲኖራቸው የሚደነግግ አንቀጽ አካቷል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአትና የማስረጃ ሕግ ረቂቅ አስመልክቶ የሕግና ፍትህ
ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና ምክረ ሀሳብ መርምሮ አፅድቋል።
