Breaking News
Home / Amharic / የትናንትናው ስብስብ mastermind ወያኔ ነች።

የትናንትናው ስብስብ mastermind ወያኔ ነች።

የትናንትናው ስብስብ mastermind ወያኔ ነች። ወያኔ ብልጥ ነች፣ ለእርሷ ተገዥና ወዳጅ የሆኗትን አሳምራ ታውቃለች። ወያኔ ከድሮም ጀምሮ አብራቸው የምትሠራውን መምረጥ ትችልበታለች።
በዚህ “ጦርነት ይቁም ሠላም ይቅደም” “የውይይት ዝግጅቷ ራሷን [ሠላማዊ] አስመስላ የቀረበችው ከልቧ ሳይሆን ቀጣይ ከአጋሮቿ ጋር ሆና ለምታደርገው ጦርነት ማስመሰያና “ሠላማዊነትን” ፈላጊ ለመምሰል ነው።

በዚህ ውይይት እነ ዘመነ ካሴም እየተናገሩ እያየን ነው። የዘመነ በዚህ ውይይት መሳተፍ ትርጉሙ የተለዬ ባይሆንም ከሕወሓትና ከኦነግ ጋር “እንሠራለን” ያለውን ነገር በፖለቲካ ቋንቋ justify ለማድረግ ነው፤
ወይም አጋር ነን ለማለት ነው።

እንደሚታወቀው፥ ዘመነ ካሴን በቀጥታ ወደዚህ ነገር ያስገባው ምክንያቶች፦
1ኛ. በፋኖ ትግል ውስጥ እርሱም ሆነ ከጀርባ የሚዘውሩት የጎጃም ብአዴኖች “የፋኖን ትግል በብቸኝነት እንመራዋለን” የሚለው ዕቅዳቸው ስለከሸፈባቸውና በትግሉ ላይ በሠሩት ሴራ ሌላው
ታጋይና ሕዝብ አንቅሮ ተፍቶ ብቻቸውን ስለቀሩ [ቢያንስ] በዚህ የወያኔ መድረክ በመሳተፍ “እኛም አለንላችሁ” ለማለትና አጋርነታቸውን ለመግለጽ ነው።

2ኛ. ሕወሓት ቀጣይ ከአጋሮቿ ጋር ሆና ለምታደርገው ጦርነት እነ ዘመነ ካሴ ቅድመ ይፋዊ ዕውቅና ለመስጠትና አጋር ሆነው [ቢችሉ] ሕወሓትን ወደ አራት ኪሎ ለመመለስ ነው።
ከሁሉ የሚገርመው የአማራ ሕዝብ ጠላት የሆነዉን ኢትዮጵያን በዘር ክልል የከፋፈለዉን የወያኔ ዋና መሪ ስብሐት ነጋን ማቅረባቸው ነው:: በጣም ያሳፍራል !
ዘመነ እስክንድር ድራሹ ይጥፋ ይላል መከታው ላይ ጦር ይልካል:: ግን ከነዚህ ነፍሰ ገዳዮች ጋር ነው ይቀርባል ::
ግን ምን ያድርጉ ? ሌላው አማራ ሁሉ ዝም ሲል እነሱ ቀደሙ ! ፋኖ እርስ በርስ ሲወነጃጀልና ሲገዳደል እነዚህ ቀድመው ተገኙ ! አይናችሁ እያየ ስልጣን ሊረከቡ ይችላሉ !

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.