Breaking News
Home / Amharic / አባሴራ፣ አባቁማር፣ አምስት አመት ሙሉ አገሪቱን አመሳት፣

አባሴራ፣ አባቁማር፣ አምስት አመት ሙሉ አገሪቱን አመሳት፣

አባሴራ፣ አባቁማር፣ አምስት አመት ሙሉ አገሪቱን አመሳት፣
አሁንም በስውርና በግልጽ የሕዝብ ዕልቂትና ስቃይ እንዲቀጥል ሰበብ እየፈለገ የአማራ ሕዝብንና መሬቱን በደም እያጨቀየ ነው፣
ኢትዮጵያ በታሪክዋ እንደአብይ አይነት ከሐዲና አጭበርባሪ ፣ ርሕራሔ የሌለው ጨካኝና አረመኔ ፣ ሴረኛና ሸፍጠኛ፣ ደካማና ልፍስፍስ፣ ብቃት የሌለውና ቅን ያልሆነ፣ ሥራውን በትክክል መሥራት የማይችልና የማይፈልግ፣ አስመሳይና እስስት ፣ ሥልጣን ወዳድ ብቻ ሳይሆን ሥልጣን አምላኪ፣ እጅግ እራሱን የሚወድና ራሱን የሚያመልክ፣ ለአገርና ለሕዝብ ምንም የማይጨነቅና ኃላፊነት የማይሰማው፣ መሪ አግኝታ አታውቅም ።
አብይ አህመድ ሁሉንም ፣ ጀነራሎቹንም፣ ፖለቲከኞችንም፣ አክቲቪስቶችንም፣ ሙሑራንንም፣ ሙዚቀኞችንም፣ወዘተረፈ በጥቅም ፣በገንዘብ ፣በመሬት እና በኮንዶሚኒየም ለመግዛት የአገርና የሕዝብ ሐብት ላይ እየተጫወተ ነው።
የኢትዮጵያ ሆይ፣ የኦሮሞ ሕዝብ ሆይ ፣ የአማራ ሕዝብ ሆይ፣
ወዘተረፈ ይሰማል ወይ? ምን ይመስላችሁዋል ?
ተግባራዊ ምላሽ ያስፈልጋል ።
Dashen Times
በተራ ጥቅም አገርና ህዝብ አይሸጥም
===========================
የጏደኞቻችሁ አፅም እሾ ሆኖ ይወጋችሗል:: እናንተን ለመደለያነት ያቀረበው መሬት ሺህ ዓመት አትኖሩበትም! እነዚህን የተሰዉ ጏደኞቻችሁን አስቡ!
እውነት አብይ አህመድ ለሰራዊታችን ቢያዝን ኖሮ ለእነዚህ የሰራዊት አባል ቤተሰቦች እርዳታ ያደርግ ነበር:: በክብር የተሰውና ቤተሰቦቻቸው በችግር የሚኖሩ
1. ኮሎኔል ዳኘ በላይ ዳንኤል
2. ኮሎኔል አማረ ሞላ በየነ
3. ኮሎኔል አልታሰብ መንግስቴ አለማየሁ
4. ኮሎኔል ለማ ታፈሰ ሽፈራው
5. ኮሎኔል ሞላ ስመኝ ደሴ
6. ኮሎኔል ባህሩ ተገኝ
7. ኮሎኔል ሞሃባ አበጀ
8. ኮሎኔል ጀማል አብዲ መሃመድ
9. ኮሎኔል የሺብር አዳነ እርቁ
10. ኮሎኔል ሚካኤ ሰረበ ይሳቅ
11. ሻለቃ አብዩ ጋሹ ጀምበሬ
12. ሻለቃ እያሱ ሽመልስ ዘውዴ
13, ኮሎኔል አለምነው ሞላ
አብይ አህመድ የመከላከያ ፋውንዴሽንን ለስልጣኑ ማራዘሚያ እየተጠቀመበት ነው:: የኢትዮጵያ ህዝብ የአገር መከላከያ ሰራዊት ጀኔራል መኮነኖችን በጥቅም ለማታለል አዲስ አበባ ውስጥ ቤትና የቤት መስሪያ ቦታ እየሰጠ ነው::
ስንት መስዋዕትነት ለከፈሉና አገራቸውን ላገለገሉ ጀኔራል መኮነኖች የቤት መስሪያ ቦታ መሰጠት ሲያንሳቸው ነው ነገር ግን እየተሰራ ያለው የሰራዊቱ አዛዦችን ለመደለልና ህዝብን ለመጨፍጨፍ ያለመውን እቅድ እንዳይቃወሙት እንጅ ለእነሱ አስቦ አይደለም:: ትህነግ አዳስ አበባ ውስጥ ለጀኔራሎች የሰጣቸውን ቦታ ታስታውሳላችሁ:: እውነት ነገ ለምትቀበሩበት መሬት ህዝባችሁን በጥቅም ልትሸጡ? ለማንኛውን መደለያው ይህንን ይመስላል
1. ለብርጋዴር ጀኔራል— ባለ 3 ክፍል ኮንዶምንየም
2. ለሜጀር ጀኔራል—500 ካሬ ሜትር መሬት
3. ለሌተናል ጀኔራል —750 ካሬ ሜትር መሬት
4. ለጀኔራል —1000 ካሬ ሜትር መሬት
5. ለፊልድ ማርሻል —1500 ካሬ መሬት አዲስ አበባ ውስጥ ተሰጥተዋል:: ቤታቸውን ደግሞ የመከላከያ ኮንስትራክሽን ሰርቶ እንዲሰጣቸው ተወስኗል::
ወንድሞቻችን ቢያን አስቡ
ኮሎኔል የሽብርን
ኮሎኔል አማረ ሞላን
ኮሎኔል ባህሩ ተገኝን ወዘተን አስቡ! በጥቅም ተጠልፋችሁ ወድቃቹ አማራንና ኤርትራን ብትወጉ ታሪክ ይፋረዳችሕል!
Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.