አሥራት:_ የካቲት 13/2012 ዓ/ም ዛሬ የካቲት 13/2012 ዓ/ም በቡራዩ ከተማ በተፈፀመ ጥቃት የከተማው ፖሊስ አዛዥ ኮሚሽነር ሰለሞን ታደሰ በጥይት መገደላቸው ታውቋል። ከኮሚሽነር ሰለሞን ጋር የነበሩ የአዲስ አበባ ዙሪያ ልዩ ዞን የልዩ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ተስፋዬ ድንቁም በጥይት ተመተው የቆሰሉ ሲሆን ወደ ሆስፒታል ተወስደው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ተብሏል። ጥቃት የተፈፀመው ከቀኑ 6 ሰዓት አካባቢ ሲሆን ሁለቱ የፀጥታ ኃላፊዎች አብረው ምሳ በመብላት …
Read More »TimeLine Layout
February, 2020
-
17 February
ወደ ሀገራችን መልሱን
የኢትዮጵያውያን ሰቆቃ የስነ ልቦና ቀውስና ችግር የሚሰማን ከሆነ ይህም ችግር ችግራችን ነው። ……….. ወደ ሐገራችን መልሱን !!! ኮሮና ቫይረስ በተቀሰቀሰባት የቻይናዋ ውሃን ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ድምፃችን ይሰማ እያሉ ነው።በቻይና የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማሕበር በማሕበራዊ ሚድያዎች የአስወጡን ቅስቀሳ ጀምረዋል። ተማሪዎቹ መንግሥት ወደ ሃገራቸው እንዲመልሳቸው በመጠየቅ ላይ ናቸው።በውሃን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ቁጥር 300 ገደማ እንደሆነ ይገመታል።አብዛኛዎቹ በስጋት ውስጥ እንዳሉና ከተማዋም ፀጥታ የዋጣት እንደሆነች ይናገራሉ። …
Read More » -
13 February
መልእክቴን ለጃዋር መሀመድ አድርሱልኝ
ስማኝ ጃዋ አየህ ጅማዎች አንድ #ንጉስ _አባ_ጅፋር የሚባሉ ሙስሊም ሆነው የጊዮርጊስ ቤተክርስቲያንን ያሰሩ በፍቅር የሚያምኑ፤ዘመኑን የቀደሙ ታላቅ መሪ ነበሯቸውና ፍርድ ያውቃሉ። ዝም ብለህ በሚያነቃቃ ንግግር ብቻ በወሬ ብቻ አታታልላቸውም።ጀግና በደንብ ለይተው ያውቃሉ፤ ባይሆን ምክር የሚሰማ ሰው ከሆነ፤ ባለህ አጭር ግዜ የፖለቲካ ቅስቀሳውን ትተህ፤ከማያልቀው ገንዘብህ ትንሽ ቆንጥረህ ለደሃው የኦሮሞ ልጆች ደብተርና ስክሪብቶ፣ሳሙናና መጽሃፍ፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ አልፎ አልፎ አስተክልላቸው ቀልዱን ትተህ፤ …
Read More » -
11 February
ለአየር ትኬት በሰባት ወራት ውስጥ ብቻ 16 ሚሊዬን ብር ወጭ ተደርጓል።
ያሳዝናል በርቀት የተማሩ ሰዎች በርቀት እያስተዳደሩ ነው። የብአዴን ባለስልጣናት ክልሉን አዲስ አበባ ተቀምጠው በርቀት ለመምራት እየሞከሩ ነው። ከሀምሌ 01/2011 ዓም ጀምሮ ከአዲስ አበባ ወደ ባህርዳር በአውሮፕላን እየተመላለሱ በደሀ ህዝብ ገንዘብ እየቀለዱ መሆኑን ምንጮች ይናገራሉ። ለአየር ትኬት በሰባት ወራት ውስጥ ብቻ 16 ሚሊዬን ብር ወጭ ተደርጓል። አዲስ አበባና ባህርዳር በተመሳሳይ ጊዜ ለእነዚሁ ባለስልጣናት 31 ሚሊዬን ብር የቤት ኪራይ ከአማራ ህዝብ ኪስ …
Read More »